Sunday, October 28, 2012

ተዋሕዶ መጠርጠር የሌለባት ሃይማኖት








ካለፈዉ የቀጠለ….

እናም ትንቢቶቹ በመሀመድ ወይም በሉተር አልያም ከእነርሱ ወዲህ ለተመሰረተ ሃይማኖት የተነገሩ ናቸዉ ተብሎ እንኳን ቢታሰብ ፍጹም የማይመስል ነገር ነዉ፡፡ምክንያቱም መስራቾቹ እነርሱ እስከሆኑ ድረስ ከመሀመድ ወይም ከሉተር በፊት ሃይማኖት አልነበረም እንዴ ? ተብሎ ቢጠየቅ መልስ አይኖርም፤ምናልባት ላለማመን ተብሎ ሌላ ነገር ካልተነገረ በቀር ማለት ነዉ ወይም በሌላ በኩል ከእነ መሀመድ እና ሉተር በፊት የነበሩ ሐዋያት ቅዱሳን ጻድቃን ሰማእታት በሙሉ እነ ሉተር ዘመን ላይ ስላልደረሱ እነዚህ ሁሉ ሃይማኖት አልነበራቸዉም ማለት ነዉ? ሰዉነታቸዉ እንደ ሽንኩርት በሰይፍ የተቀረደደዉ ፤ በእሳት የተቃጠለዉ ፤ አጥንታቸዉ  እየተፈጨ በንፋስ የተበተነዉ ፤ ቆዳቸዉ ተገፎ አቅማዳ እስኪሆን ድረስ ያደረሳቸዉና ያን ሁሉ ሰማእትነት ይከፍሉ የነበረዉ ገና ወደፊት ፍር ለሚመሰርተዉ ሃይማኖት ነበር ማለት ነዉ?




Sunday, October 21, 2012

ተዋሕዶ መጠርጠር የሌለባት ሃይማኖት



ትንቢቶች ሁሉ መፈጸማቸዉ ግድ ነዉ፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ህግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለእኔ የተጻፈዉ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል (ሉቃ24፤44) እንዳለ ስለርሱ የተነገሩ ትንቢቶችን በሙሉ እርሱ ፈጽሟቸዋል፤ ነቢያትና ሐዋርያት ስለመጪዉ ጊዜ  የተናገሩትም ትንቢት ቅንጣት ታክል እንኳን ሳትፈጸም አትቀርም፡፡ ስለ ሰዎች እምነትና ክህደት የተነገሩ ትንቢቶች ተፈጽመዋል፡፡እየተፈጸሙም ነዉ ገና ወደ ፊትም ይፈጸማሉ፡፡
ሐዋርያት “በግልጽ በለኞች ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ መናፍስትንና በዉሸተኞች  ግብዝነት የተሰጠዉን የ አጋንንትን ትምህርት እያደመጡ ሃይማኖትን ይክዳሉ”  (1ጢሞ4፡1) <<በቅዱሳን ነቢያትም ቀድሞ የተባለዉን ቃል በሐዋርያቶቻችሁም ያገኛችሁትን የጌታንና  የመድሃኒታችንን ትዕዛዝ እንድታስቡ በሁለቱ  እያሳሰብኳችሁ ቅን ልቡናችሁን አነቃለሁ፡፡በመጨረሻዉ ዘመን እንደራሳቸዉ ምኞት የሚመላለሱ ዘባቾች በመዘበት እንዲመጡ ይህን በፊት እወቁ>>(2ጴጥ3፤2) የሚሉት ትንቢቶች ሁሉ የግድ መፈጸም አለባቸዉ፡፡<<ክህደት  ትጠፋለች ሃይማኖት ግን ለዘላዓለሙ ትጸናለች>>ሲራ40፤12


“ወኢንህድግለነ ማህበረነ”መሰባሰባችንን አንተዉ (ዕብ 10፡25)




ከፍረት አለም ጀምሮ ቅዱሳን መላእክት ሆኑ የሰዉ ልጆቸ እግዚአብሄርን በህብረት  ሆነዉ እንደየተፈትሮአቸዉ እንደሚያመልኩት መፅሃፍት ያስረዱናል ፡፡በብሉይ  ኪዳን አይሁድ ለእግዚአብሄር በለዩት ስፍራ በማህበር በመሰባሰብ እግዚአብሄርን ያመልኩት ነበር፡ ለስሙም መስዋእትን በፊቱ ያቀርቡ ነበር ፡ ፡በሐዲስ ኪዳንም ሐዋርያት እንደ አንድ ቃል ተናጋሪ እንደ አንድ ልብ መካሪ  በመሆን በህብረት ይጸልዩና በሰሙ ይሰበሰቡ እንደነበር ቅዱስ ሉቃስ በሐዋርያት ስራ ላይ ዘግቦት እናነባልን፡፡ ሐዋ4፡32   ይህን ማህበርም  ለእዉነተኖች ክርስቲያኖች አስረክበዉ አልፈዋል፡ ፡