Thursday, October 31, 2013

ባልንጀራዬ ማነው? ሉቃ 10፡29



 


ባልንጀራዬ ማነው? ሉቃ 10፡29
ምንም እንኳን ሁሉም ሰው ከአንድ የአዳም ዘር የተገኘ ቢሆንም ሲወርድ ሲዋረድ በመጣው የሰው ልጆች በአከባቢ በቋንቋ ፣ በአኗኗር ፣ በባሕል ወዘተ መለያየት እንዲሁም የቁጥር መብዛት የተነሣ፤ እስከተወሰነ የዘር ግንድ ድረስ ያለውን የሥጋ ዘመዴ ብሎ ሲጠራ ሌላውን ደግሞ ባዕድ ይለዋል፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው ብቻውን ወይም የሥጋ ዘመዴ ካላቸው ጋር ብቻ ስለማይኖር በአጠቃላይ በማኅበራዊ ሕይወቱ፣ በሥራው ፣ በትምህርቱ ከብዙ ዓይነት ሰዎች ጋር ይገናኛል አብሮም ይኖራል፡፡ በእነዚህ አጋጣሚዎችም በሃሳብ፣ በዓላማ ከሚመስሉት ጋር ባልጀርነትን (ጓደኝነትን) ይመሠርታ፡፡ በብዙ አጋጣሚ እንደሚታየውና በጽኑ ፍቅር ላይ የተመሠረተ ጓደኝነት ከሆነ ከሥጋ ዝምድና ቢበልጥ እንጂ የማያንስ ችግርን ደስታን ምስጢርን በጋራ የሚካፈሉበት፣ ለአንተ ለአንቺ የሚባባሉበት ትልቅ የሕይወት ክፍል ነው፡፡

Tuesday, October 29, 2013

‹‹እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተጭኖ ወደ ግብፅ ይመጣል›› (ኢሳ 19-1)

ክፍል ሦስት     

ሰባዓ ሰገል ከሩቅ ምስራቅ ተነስተው ‹‹የተወለደው የአይሁድ ንጉስ ወዴት ነው?›› እያሉ በመጡ ጊዜ ሄሮድስ ደነገጠ ‹‹ንጉስማ ከሆነ ንጉሥ ሳይገድል ይነግሳልን?›› ብሎ የካህናትንም አለቆች ሰበሰበ ክርስቶስ ወዴት እንዲወለድ ጠየቃቸው በቤተልሔም መሆኑን ነገሩት ከዚያ በኋላ ሰብአ ሰገልን ጠርቶ ከአገኙት ተመልሰው እንዲነግሩትና ሄዶ እንደሚሰግድለት መክሮ ላካቸው፡፡ እነርሱ ግን ወደ ሄሮድስ እንዳይመጡ በሕልም ተረድተው በሌላ መንገድ ወደ አገራቸው ሄዱ፡፡ ለዮሴፍም መልአክ በሕልም ታይቶ ሕፃኑንና እናቱን ይዞ ወደ ግብፅ እንዲሸሽ አደረገው (ማቴ 2፡15) እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም ጌታችንን አዝላ ፀሐይና ብርድ እየተፈራረቀባት የአሸዋው ግለት የመንገዱ ርዝመት ሳይበግራት ከእየሩሳሌም ተነስታ እስከ ግብፅና ኢትዮጵያ ድረስ ለሦስት ዓመታት ያህል በመንከራተትና ልጇን ከሚፈታተኑ ጠላቶች ሁሉ አቅፋ ሸፍና በመከለሏ ደመና ተብላለች፡፡ ከዚህም የተነሣ አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለምን ወደ ግብፅና ኢትዮጵያ ተሰደደ ለሚለው ጥያቄ ይህ የኢሳይያስ የትንቢት ቃል ‹‹እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና ተጭኖ ወደ ግብፅ ይመጣል›› (ኢሳ 19-1) የሚለው አንዱና የመጀመሪያው ምክንያት ነው፡፡


Monday, October 28, 2013

‹‹ናሁ እግዚአብሔር ይነብር ዲበ ደመና ቀሊል ወይመጽዕ ውስተ ግብፅ›› ኢሳ 19÷1

ክፍል ሁለት

 

                                                                   
ባለራእዩ ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ሴቱትም ሺህ ከሁለት መቶ ስድሳ ቀን በዚያ እንዲመግቡአት በእግዚአብሔር ተዘጋጅቶላት ወደ ነበረው ሥፍራ ወደ በረሃ ሸሸች›› (ራዕ 12፡6) እንዲል አዛኝት እናት ድንግል ማርያም ልጇን ወዳጇን ይዛ ስደት ተነሣች፣ የስደተኞችን መፅናኛ (ምስካዬ ኅዙናን) ይዛ ተሠደደች ዓላማትን የፈጠረውን ጌታ ታቅፋ አሽዋ ለአሽዋ ተንከራተተች፣ ፍጥረታትን በየሥፍራቸው የወሰነውን እርሱ ግን ቦታና ጊዜ የማይወስነውን የእግዚአብሔር ልጅ እግዚአብሔር የተባለው ልጇን ለተወሠኑ ጊዜያት በተወሠነ ስፍራ ታቆየው ዘንድ አዝላው ተሰደደች ለሰው ልጆች ክፉ ቀንን የሚያሳልፈውን አምላክ አዝላ ክፉ ቀን እስከሚያልፍ ተሰደደች ‹‹ዘንዶውም ወደ ምድር እንደተጣለ ባየ ጊዜ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሰደዷት ከእባቡም ፊት ርቃ አንድ ዘመን ዘመናትም የዘመን እኩሌታ ወደ ምትመገብበት ወደ ሥፍራዋ ወደ በረሃ እንድትበር ለሴቲቱ ሁለት የታላቅ ንስር ክንፎች ተሰጣት›› (ራዕ 12፡13-15) ተብሎ እንደተፃፈ ፈጣን ደመና ናትና በተሰጣት ክንፍ እየበረረች ቀድሞ በነቢዩ በኢሳይያስ እንደተፃፈ ‹‹ሰማይ ዙፋኔ ምድር የእግሬ መረገጫ ነው›› (ኢሳ 66፡1) ያለ አምላክን ሥጋና ደምን ተዋህዶ ሕፃን ሆኖ ከማህፀኗ በመወለዱ አንድ ጊዜ በእቅፏ አንድ ጊዜ በጀርባዋ እያዘለች የግብፅን በረሃ አቋርጣ ወደ ኢትዮጵያና ወደ ግብፅ ተሰደደች ኢትዮጵያም ተባረከች ኢትዮጵያንም ተደሰቱ እግዚአብሄርንም አመስግኑ ይህንንም በትንቢት መነጽር ተመልክቶ የእግዚአብሔር ነቢይ እንባቆም ‹‹የኢትዮጵያ ድንኳኖች ሲጨነቁ አየሁ የምድያም ሀገር መጋረጃዎችም ተንቀጠቀጡ›› (ዕንባ 3፡7) በማለት ሕፃኑንና እናቱን ለመቀበል በትህትናና በፍቅር መቅደሱን ሞልተው የነበሩትን ኢትዮጵያውያንን ጠቅሶ መዝግቦልናል፡፡








Saturday, October 26, 2013

‹‹ናሁ እግዚአብሔር ይነብር ዲበ ደመና ቀሊል ወይመጽዕ ውስተ ግብፅ›› ኢሳ 19÷1

 
 

 
ሰማይና ምድር በጉምና በጭጋግ ተሸፍነው ከላይ ዝናም እየመታን ከታች ጎርፍ እየጠለፈን በብርድ እየተንቀጠቀጥን ወርኃ ክረምት አልፎ ፀሐይ ከምስራቅ የብርሀን ጨረሯን ፈንጥቃ ጋራ ሸንተረሩ በአደይ አበባ ደምቆ አፍላጋት ከየቦታው እየተፍለቀለቁ የአዲስ ዘመን ሀሴት በልባችን በፈነደቀበት የመፀው ወራት ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ‹‹እንሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና እየበረረ ወደ ግብፅ ይመጣል›› ይለናል፡፡ በመሠረቱ ነቢዩ ስለክረምቱ ደመና ሳይሆን ይህንን ኃይለ ቃል የተናገረው ሕዝብ አዳምን የሕይወት ውሃ ያጠጣ እውነተኛ ዝናብ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ስላስገኘች አማናዊት ደመና ቅድስት ድንግል ማርያም ስደት በሚስጢር ለመናገር ፈልጎ ነው፡፡