Friday, December 27, 2013

‹‹ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ›› (ማር 13፡15)









     ቀድሞ ከእግዚአብሔር ለቅዱሳን አንድ ጊዜ የተሰጣቸውና በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ጸንታ የተመሠረተችው በሰማዕታትም ደም ያሸበረቀችው ቅዱስት ቤተክርስቲያን ከተመሠረተችበት ዕለት አንስቶ በውጊያ ላይ ብትሆንም እንኳ ሁል ጊዜ ድል ታደርጋለች እንጂ ተሸንፋ አታውቅም ታላቁ የቤተ ክርስቲያን አባት ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለቤተክርስቲያን በገለጸበት ድርሳኑ ‹‹ሰውን በትታገልና በትዋጋ ታሸንፈዋለህ ወይም ያሸንፍሃል ቤተክርስቲያንን ግን ለማሸነፍ አይቻልም፤ ቤተክርስቲያን ሁል ጊዜ ትዋጋለች ተሸንፋ ግን አታውቅም ዲያብሎስ ዝናሩን አራገፈ፣ ቀስቱን ጨረሰ ቤተክርስቲያንን ግን አልጎዳትም›› ብሏል፡፡
ርቱዐነ አንደበት የሆኑ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን መናፍቃንን በቃልም ሆነ በጽሑፍ ሲዋጉ ኖረዋል የአበውን አሰረ ፍኖት የተከተለ ይህ ትውልድም የአባቶችን አደራ ተቀብሎ በግብር ሊመስላቸው ይገባል፡፡







Thursday, December 26, 2013

"እነሱ በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ" (ዕብ 11÷33)





የጽድቅ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ለቤዛነት ቀን ለታተሙት በሜሮን ለከበሩት በልጅነት ክብር ለተጠሩት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተሰኙ ለዕብራውያን ሰዎች በሃይማኖት እንዲቆሙ በክርስቶስ ደም በተዋጀችው በሐዋርያትና በነቢያት መሠረትነት ላይ በታነጸችው በመጀመሪያ እምነታቸው እንዲፀኑ ሲያስተምር ይህንን ቃለ ተናግሮታል፡፡ እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው አለ ሐዋርያው፤ አዎ እምነት የማይታየው እንደሚታይ የማይቻለው እንደሚቻል የማይገፋው እንደሚገፋ የሚያስረዳ ረቂቅ መሣሪያ ነው፡፡ እምነት የረቀቀውን የሚያጎላ የተሰወረውን የሚገልጽ የራቀውን የሚያቀርብ እጉሊ መነጽር ነው፡፡

Wednesday, December 25, 2013

‹‹እነሱ በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ›› ዕብ 11፡33




‹‹እነሱ በእምነት የእሳትን ኃይል አጠፉ›› ዕብ 11፡33
የጽድቅ ሐዋርያ ቅዱስ ጳውሎስ ለቤዛነት ቀን ለታተሙት በሜሮን ለከበሩት በልጅነት ክብር ለተጠሩት በወልድ ውሉድ በክርስቶስ ክርስቲያን ለተሰኙት ለዕብራውያን ሰዎች በሃይማኖት እንዲቆሙ በክርስቶስ ደም በተዋጀችው በሐዋርያትና በነቢያት መሠረትነት ላይ በታነጸችው በመጀመሪያ እምነታቸው እንዲፀኑ ሲያስተምር ይህንን ቃል ተናግሮታል፡፡ እምነትም ተስፋ ስለምናደርገው ነገር የሚያስረግጥ የማናየውንም ነገር የሚያስረዳ ነው አለ ሐዋርያው አዎ እምነት የማይታየው እንደሚታይ የማይቻለው እንደሚቻል የማይገፋው እንደሚገፋ የሚያስራዳ ረቂቅ መሳሪያ ነው እምነት የረቀቀውን የሚያሳይ የተሰወረውን የሚገልጽ የራቀውን የሚያቀርብ አጉሊ መነጽር ነው ለዚህም ነበር አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዘመነ ሥጋዌ በሚያስተምርበት ዘመን ለሚያምን ሁሉ ይቻላል ያለው ማር 9፡23


Thursday, December 19, 2013

‹‹ፆምን ቀድሱ›› (ኢዩ1፡14)









‹‹ፆምን ቀድሱ›› (ኢ 1፡14)
አምላካችን እግዚአብሔር በነቢዩ በኢዩኤል ላይ አድሮ የእግዚአብሔር በረከት ከእስራኤል ጠፍቶ በምትኩ መቅሠፍትና መዓት ረሃብና ቸነፈር በመጣባቸው ጊዜ (ኢዩ 1፡1-13) ፆምን ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤት ሰብስቡ ወደ እግዚአብሔር ጩኹ (ኢዩ 1፡14) አላቸው፡፡ ለመሆኑ ፆምን መቀደስ ማለት ምን ማለት ነው? እንዴትስ ይፈጸማል?