Sunday, September 28, 2014

“ዕፀ መስቀሉ ከየት መጣ”


“ዕፀ መስቀሉ የት መጣ”

የመስቀሉ ቃል ለሚጠፉት ሞኝነት ለእኛ ለምንድን ግን የእግዚአብሔ ኃይል ነውና እንደተባለው በቆሮ 1÷18/ ክርስቲያኖች ኃይላችን፣ መመኪያችን፣ ነፍሳችን መዳኛና የምንጸናበት መስቀል እናምናለን፡፡ ነብየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት “እግሮቼ በሚቆሙበት ሥፍራ እንሰግዳለን” እንዳለም /መዝ 131÷7/ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመስቀል ላይ ውሎ እኛ ለሠራነው ኃጢአት ካሣ እንደሆነ እያሰብን እንሰግድለታለን፡፡ በልባችን፣ በሰውነታችንና በቤታችን እንስለዋለን፡፡ በአባቶቻችን እንባረክበታለን፡፡ እንደትምህርታችን የድኅነታችን ብርሃን የበራበት ይህ መስቀል የእንጨት ነው፡፡ እንጨት ከመሆኑ ጋርም አንድም ለመስቀሉ ካላቸው ፍቅር ወይም ታሪክን በተረት ቀርፀው ከማስቀረት ልማዳቸው የተነሣ ይህ መስቀል ከየት መጣ? ለሚለው አባቶች የሚተርኩት አንድ ታሪክ አለ፡፡ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡፡

Thursday, September 25, 2014

ለሚፈሩህ ምልክትን ሰጠኃቸው

                            


ከላይ በርእስነት ያነሣነውን ኃይለቃል በመንፈስ ቅዱስ ገላጭነት ነቢዩ ዳዊት ተናግሮታል፡፡ አባቶች ነገሮች ከመፈጸማቸው በፊት አስቀድሞ ትንቢት አላቸው ሲሉ ትንቢት ይቀድሞ ለነገር" እንዲሉ፡፡ (መዝ. ፶፱÷፬)

የእግዚአብሔር ወዳጅ፣ መዝሙረኛው ዳዊት በትንቢት መነጽርነት የተረዳው ምስጢር ቢኖር መድኃኔዓለም ክርስቶስ የተሰቀለበት ክቡር መስቀል የሚያድን፣ ከሰይጣን የሚታደግ፣ ከክርስቲያኖች ጋሻ ሆኖ የተሰጠበ በረከት መሆኑን ነው፡፡ ነቢዩ የመስቀሉን አዳንነት የተገነዘበው በተሰጠው የትንቢት ጸጋ ነው፡፡ በቀራንዮ መሥዋዕት የሆነው ቸሩ አምላክ ክቡር መስቀሉን ሊቀድሰው ስለፈለገ ቅዱስ ሥጋውን ቆረሰበት ክቡር ደሙን አፈሰሰበት፡፡

Wednesday, September 10, 2014

‹‹አዲስ ልብንና አዲስ መንፈስን ለእናንተ አድርጉ›› (ሕዝ 18፡31)



መልካም አዲስ ዓመት

ኃይለ ቃሉን የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሕዝቡን በሚመክርበት ዘመን ከአበይት ነቢያት አንዱ በሆነው በነቢዩ በሕዝቅኤል በኩል ስለብዙ ነገር ተናግሮታል፡፡ ለጊዜው ለእስራኤል ዘሥጋ ይነገር እንጂ ፍጻሜው ግን እኛም እንማርበት ዘንድ ተመዝግቦልናል፡፡ በመሆኑም የዚህ ጽሑፍ ዋና መልዕክትና መሠረታዊ ዓላማ በምድራዊው የኮንትራት ኑሯችን በዘመን ተሰፍሮና ተወስኖ በተሰጠን ዕድሜ በተለይም በቀሪ ጊዜያችን አሮጌውንና የዛገውን ልብ አውጥተን አዲስ ልብን ገንዘብ እንድናደርግና በአዲስ ሕይወት እንድንመላለስ ማሳሳብ ነው፡፡