Friday, April 24, 2015

ሰማዕትም ሆኑ ማዕተብን አስረው






በዚህ ሳምንት እንኳን
እባካችሁ ተውን
የኢትዮጵያዊነት ክብራችን ተነክቶ
የሥላሴ ህንፃ ፈርሶ ተንኮታክቶ
እምነት በሌላቸው በአህዛብ ተዋርደን
ተንቀናልና መሳለቂያ ሆነን

አስብ የሆነብን





ጊዜ የሰጠው ቅል ዓለቱን ሠበረ
የዓለቱን ልጆች እጅና እግር አሰረ
ርስታችን ሁሉ ገብቶ መዘበረ
ኀያላንን ገድሎ በይፋ ፎከረ