Tuesday, September 29, 2015

ተዋሕዶ

አዲስ መጽሐፍ በገበያ ላይ



(ከመጽሐፋ  ደ)

     ትንቢቶች ሁሉ መፈጸማቸዉ ግድ ነዉ፡፡ አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእናንተ ጋር ሳለሁ በሙሴ ህግና በነቢያት በመዝሙራትም ስለእኔ የተጻፈዉ ሁሉ ይፈጸም ዘንድ ይገባል (ሉቃ24፤44) እንዳለ ስለርሱ የተነገሩ ትንቢቶችን በሙሉ እርሱ ፈጽሟቸዋል፤ ነቢያትና ሐዋርያት ስለመጪዉ ጊዜ  የተናገሩትም ትንቢት ቅንጣት ታክል እንኳን ሳትፈጸም አትቀርም፡፡ ስለ ሰዎች እምነትና ክህደት የተነገሩ ትንቢቶች ተፈጽመዋል፡፡እየተፈጸሙም ነዉ ገና ወደ ፊትም ይፈጸማሉ፡፡

በምስጢረ ጥምቀት ምስጢረ ሥላሴ ተገለጠ

በምስጢረ ጥምቀት ምስጢረ ሥላሴ ተገለጠ


በቅዱሳት መጻሕፍት በጉልህ ተመዝግቦ እንደምናገኘው አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እስከ 30 ዓመቱ  ድረስ ለእናቱ ለ ቅድስት ድንግል ማርያም እየታዘዛትና እየተላላከ አደገ ( ሉቃ 2፣) በ30 ዓመቱ ግን ሰማይና ምድር በመሀል እጆቹ የተያዙ አምላክ እንደ ተራ ሰዎች በፈለገ ሄኖን በማዕዶት ዮርዳኖስ ለመጠመቅ ሄደ በጥንተ ፍጥረት የእግዚአብሔር መንፈስ በውሀ ላይ ሰፎ ነበር        (ዘፍ፩፣፪) በሐዲስ ኪዳን ደግሞ ከሶስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ ከባህርይ አባቱ ከአብ ከባህርይ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ የተካከለ እሱ መድሐኔዓለም ክርስቶስ በእደ ዮሐንስ በባህረ ዮርዳኖስ በመጠመቅ ለውኃ የበለጠ ኃይል ሰጠው :የባርነት ደብዳቤ በዮርዳኖስ ነበርና ዕዳ በደላችን  ይደመስስ ዘንድ በባህረ ዮርዳኖስ በትህትና በባሪያው እጅ ይጠመቅ ዘንድ ወደ ውሃው ገባ፡፡

Wednesday, September 23, 2015

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥያቄዎች


የሚከተሉት አዛምድ

1         እግዚአብሔርንም ለመሰደብ ስሙንና ማደሪያውንም                                    ይ) ራዕ 13-6
             በሰማይ የሚያድትን ሊሳደብ አፉን ከፈተ፡፡                                                      

2         እንዲሁም  እነዚህ ሰዎች ደግሞ እያለመ ሥጋቸውን ያረክሳሉ                          የ) ዕብ 13-9

          ጌትነትንም ይጥላሉ ሥልጣን ያላቸውንም ይሳደባሉ ፡፡

Monday, September 21, 2015

ጼዴንያ ማርያም


 
" ሰላም ለሥዕልኪ እንተ ሠዓላ በእዱ፡፡ ሉቃስ ጠቢብ እምወንጌላውያን አሐዱ፡፡ አመ ተቀብዑ ማርያም እምሐፈ ሥዕልኪ ቅብዐ ናርዱ፡፡ "
ጼዴንያ በምትባል ሀገር ማርታ የምትባል ደግ ሴት ነበረች፡፡ ይህች ደግ ሴት በቤቷ ትልቅ አዳራሽ ሰርታ እንግዶችን እንደ... አባታችን አብርሃም ተቀብላ አብለታ አጠጥታ ማደሪያ ቦታም ሰጥታ ታስተናግድ ነበር፡፡ አባ ቴዎድሮስ የሚባል ኢትዮጵያዊ መነኩሴ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሔድ መሽቶበት ከማርታ ቤት በእንግድነት አድረ ጠዋት ሲሔድ ሲነሣ ወደ ኢየሩሳሌም እንደሚሄድ ሲነግራት የእመቤታችንን ሥዕል ገዝተህ አምጣልኝ ዋጋውን ልስጥህ አለችው፡፡ ገንዘቡን ሥዕሉ ን ሳመጣልሽ ትሰጪኛለሽ ብሏት ሄደ፡፡
ቦታዎችን (መካናትን) ተሳልሞ ሥዕሉን ረስቶ ሳይገዛ ሲመለስ « አደራ ጥብቅ አይደለምን) ያቺ ሴት አደራ ያለችህን ለምን ረሳህ» የሚል ድምጽ ሰማ ተመልሶ ሄዶ ገዝቶ በረሃ በረሃውን መጓዝ ጀመረ፡፡ በመንገድም እየተጓዘ አንበሳ ሊበላው አየሮጠ ወደ እሱ ሲመጣበት አየ መነኩሴው አንበሳውን ከመፍራት የተነሣ ደነገጠ ተንቀጠቀጠ ደንግጦ ቁሞ ሳለ ያች ሥዕል ከአንበሳው ጩኸት ሰባት እጅ በሚበልጥ አስፈሪ ድምጽ ጩሃ ተናገረች፡፡ ያን ጊዜ አንበሳው ደንግጦ ፈጥኖ ሸሸ፡፡

“አዎ ድንግል ማርያም ተነሥታለች ፤ ዐርጋለች!”

                    
          
 “አዎ ድንግል ማርያም ተነሥታለች ፤ ዐርጋለች!”
‹‹በቅድሚያ በመላው ዓለም ለምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን ሁሉ እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም በዓለ ትንሣዔ ወዕርገት አደረሳችሁ››
በቀጥታ ወደ መነሻ ርዕሴ ከመግባቴ በፊት ጌታችን በወንጌሉ ‹‹አፌን በምሣሌ እከፍታለሁ………ያለ ምሳሌም አልተናገራቸውም››(ማቴ 13፡34-35) እንዳለ ፤ አበውም ‹‹ነገር በምሳሌ›› እንዳሉት ነውና እርሱን ላስቀድም፡- ‹‹አንድ ሕጻን የድንግል ማርያም ፍቅር በልቡናው ሰርጾበት “አሟሟትሽ በጥር ነሐሴ መቃብር” ፣ “ዐርጋለች ድንግል ተነሥታለች” እያለ ይዘምራል፡፡ ይህን የሰማ አንድ መናፍቅ ሕጻንነቱን አይቶ ለማሳት “ድንግል ማርያም ዐርጋለች ተነሥታለች እያልህ የምትዘምር መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንዲህ የሚል ነገር እኮ አልተጻፈም” ይለዋል፡፡ ሕጻኑ ግን የተቀደሰ ነበርና “ ተጽፏል እንጅ እንዴት አልተጻፈም ትላለህ?” ብሎ ይመልስለታል፡፡ መናፍቁም መግቢያ ቀዳዳ ያገኘ ስለመሰለው “አቡሽዬ መጽሐፍ ቅዱስ ይኼውልህ እስኪ ተነሥታለች የሚል አሳየኝ?” ይለዋል፡፡ አቡሽዬ ግን መጽሐፉን ሳይቀበል “ከመሞትና ከመነሣት የቱ ይቀድማል?” በማለት መናፍቁን የሚያስደነግጥ ጥያቄ ጠየቀ፡፡ መናፍቁም “እንዴ መሞት ነዋ!” ብሎ መለሰለት፡፡ አቡሽዬም “እንግዲያውስ መሞቷን ከያዝከው መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አሳየኝ ፤ አንተ መሞቷን ስትነግረኝ ያን ጊዜ እኔ ደግሞ መነሣቷን እነግርሃለሁ” አለው፡፡ መናፍቁም ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ማግኘት ስላልቻለ አፍሮ በአቡሽ ተሸንፎ ሔዷል›› መናፍቃን ድንግል ማርያም መሞቷን ያምናሉ ትንሣዔዋን ግን አያምኑም !!! ሞታለች የሚለው ሳይጻፍ ካመኑ ተነሥታለች ብሎ ማመን ለምን ተሳናቸው??? አንድም አልተነሣችምን ያምናሉ ተነሥታለችን ግን ይክዳሉ! አልተነሣችምን ያመነ ሕሊናቸው ተነሥታለችን ማመን ለምን ተሳናቸው???ክፋት እንጂ!!! እኛስ መጽሐፍ ቅዱስን እና አዋልድ መጻሕፍትን ተጠቅመን ፅንሰቷን ነሐሴ 7፣ ልደቷን ግንቦት 1፣ እረፍቷን ጥር 21፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ነሐሴ 16 ቀን ነው እንላለን፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በልጇ ዓርአያነት በሦስተኛው ቀን (እሑድ ተቀብራ ማክሰኞ)ተነሥታ ወደ ሰማይ ዐርጋለች፡፡ ወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ ላይ እንዳሰፈረው “ታላቅ ምልክትም በሰማይ ታየ ፀሐይን ተጐናፅፋ ጨረቃ ከእግሮቿ በታች ያሏት አሥራ ሁለት ከዋክብት የሆነላት አንዲት ሴት ነበረች” ራዕይ 12÷1 ፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ያረፈችው በ49 ዓ.ም ሲሆን ቅዱስ ዮሐንስ ደግሞ ይህንን ራዕይ የተመለከተው እርሷ ካረፈች ከብዙ ዓመታት በኋላ ነው፡፡ ምን አልባትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ አርዮሳውያን(መናፍቃን) አባባል ሞታ ቀርታ ቢሆን ኖሮ ቅዱስ ዮሐንስ በሥላሴ ዙፋን እንዴት ተመለከታት??? ያስተውሉ “ታላቅ ምልክት በሰማይ ታየ ” ነው ያለው :: በሰማይ ማለቱ እመቤታችን ሞትን ድል አድርጋ መነሣቷንና በሠማያት በክብር ዙፋን መቀመጧን ለመግለፅ ነው፡፡ ደግሞም ከርሷ ውጪ በእንዲህ ባለ ልዩ ክብር ያጌጠች ሴት በሠማያት የለችም !!! ምንም በማያሻማ መልኩ ቅዱስ ዮሐንስ በራዕዩ ድንግል ማርያምን ተመልክቷታል፡፡በተጨማሪም “በወርቅ ልብስ ተሸፋፍናና ተጐናፅፋ ንግሥቲቱ በቀኝህ ትቆማለች” መዝ 44(45)÷9 :: በማለት የመንፈስ አባቷ ቅዱስ ዳዊት አስቀድሞ እንደተነበየ በክብር ተነሥታ በልጇ ቀኝ መቀመጧን ተናግሯል ፡፡ እኛም እንናገራለን ፤ እንመሰክርማለን !

ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ


†††ገድለ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ†††
አንድ አምላክ በሚሆኑ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አምነንና ጸንተን ንጉሠ ሰማይ ወምድር ኢየሱስ ክርስቶስ በአማላጅነቷ ይቅርታን የምታሰጥ ለመሆኗ ቃል ኪዳን የገባላትን የክርስቶስ ሠምራን ገድል እንጽፋለ...ን፡፡ የእናታችን የክርስቶስ ሠምራ የትውልድ ሀገሯ ሸዋ ቡልጋ ልዩ ስሙ ቅዱስ ጌየ የተባለ ቦታ ነው፡፡ የአባቷ ስም ደረሳኒ የእናቷ ስም ዕሌኒ ይባላል፡፡ እኒህም ቅዱሳን ሰዎች ደጋጎች እግዚአብሔርን የሚፈሩ በሐይማኖት የጸኑ በበጎም ምግባር የከበሩ ነበሩ፡፡ ይህችንም ከእግዚአብሔር የተመረጠችና የተመሰገነች ልጅ ከወለዱ በኋላ በክብርና በስርዓት አሳድገው የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ትእዛዝ እያስጠኑ ብሉይ ከሐዲስ አስተማሯት፡፡ከዚያም የመኳንንት የመሳፍንት ልጅ ናትና ለኢየሱስ ሞዓ ልጅ ሠምረ ጊዮርጊስ ለሚባል ሰው አጋቧት፤ እሷም ዐስር ወንዶች ሁለት ሴቶች ልጆች ወለደች እኒያንም ልጆቿን በክብር በስርዓት አሳድጋ አስተማረቻቸው፡፡ በዘመኑ ዐጼ ገብረ መስቀል የሚባል ደግ ንጉሥ ነበረና ደግነቷን ዐይቶ ዝናዋን ሰምቶ አትርሽኝ ብሎ ፪፻፸፪ አገልጋይ ላከላት እርሷም ይህማ ከንቱ ውዳሴ ሊሆንብኝ አይደለምን መጽሐፍ ቢሆን ይነበብበት ይጸለይበት ገንዘብ ቢሆን ይመጸወት ነበር ብላ ወደ እግዚአብሔር አመለከተች፡፡

ዕረፍቱ ለሊቀ ነቢያት ሙሴ


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
መስከረም 8-የሊቀ ነቢያት ሙሴ ዕረፍቱ ነው፡፡ ይኸውም 40 ዓመት በሆነው ጊዜ አንዱ ግብጻዊ ዕብራዊውን ሲገድለው አይቶት ለወገኑ ተበቅሎ ግብጻዊውን ገድሎ ወደ ምድያም አገር ማለትም ወደ ኢት...ዮጵያ መጥቶ የካህኑን የዮቶርን ልጅ አግብቶ ሁለት ልጆችን ወለዶ በኢትዮጵያ 40 ዓመት ከኖረ በኃላ የዮቶርን በጎች እየተበቀ ሳለ እግዚአብሔር በቁጥቋጦ ውስጥ በታላቅ ራእይ ተገልጦለት እስራኤልን ከግብጽ እንዲያወጣ ነግሮት ሄዶ በተአምራት 10 መቅሰፍታት አምጥቶ ነጻ ያወጣቸው ነው፡፡
ዳግመኛም ዛሬ የመጥምቁ ዮሐንስ አባት የበራክዩ ልጅ ካህኑ ዘካርያስ በሰማዕትነት ያረፈበት ዕለት ነው፡፡
"ክርስቶስን አምላክ አትበል" በማለት አንድ ከሃዲ መኮንን በእጅጉ ካሠቃየው በኋላ አንገቱን በሰይፍ የቆረጠው የሰማዕቱ የቅዱስ ሉክዮስም ዕረፍቱ መስከረም 8 ነው፡፡