Wednesday, September 14, 2016

በዚች ዓለት ላይ ቤተ ክርስቲያኔን እሰራለሁ የሲዖል ደጆችም አያናውጡአትም። ማቴ ፲፮፣ ፲፰



ሰኔ ፳ ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፊሊጶስ ቂሳሪያ ከሦስት አዕባን (ዓለቶች ) ለእመቤታችን መታሰቢያ ይሆን ዘንድ በስሟ ቤተ ክርስቲያንን ካነጸ በኋላ ሰኔ ፳፩ ቀን ቅዳሴ ቤቷ የከበረበት ዕለት ነው። በማቴዎስ ወንጌል ፲፮ ፣፲፫ ኢየሱስም ወደ ፊሊጶስ ቂሳሪያ አገር በደረሰ ጊዜ ደቀመዛሙርቱን ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል ? ጌታችን ስለራሱ ሰዎች የሰውን ልጅ ማን ይሉታል አለ? ከእመቤታችን በነሳው ሥጋ፣ ከእኛ ከአዳም ልጆች በነሳው ሥጋ ራሱን የሰው ልጅ እያለ ይጠራልና። እምነ ፅዮን ይብል ኩሉ ሰብዕ፣ ወብእሲ ተወልደ በውስቴታ።(መዝ፹፮፣፭) 

የኢትዮጵያውያን እንቆቅልሽ መፍትሔ






ብዙዎቻችን በመንፈሳዊ ድርቀት ተይዘናል። ደስታና እረፍት ጥለው ከሸሹ ቀናት ተቆጥረዋል። ሁሉም ሰው ውስጡ ይቆዝማል። ለወዳጁ ቢያማክር እሱም የባሰ ውስጡ የኃዘን ትርምስምስ አለ። ባለን ገንዘብ ደስታ ይሰጡኛል ብለን ወደ ምናስባቸው አቅጣጫም ብናዘግም ዓለም የኛን ደስታ ሙሉ ለማድረግ አቅም የላትም። እናም ትርፍ አልባ ኪሳራ ሆነን ወደ መጣንበት እንመለሳለን። የሁሉንም ቤት እንደፈረኦን ዘመን የግብፃውያን ጓዳ ኃዘን አንኳኩቶታል።
ችግሮቻችን ደግሞ ህብረ ቀለማቸው መብዛቱ አንዱን ሳንወጣው ሌላው ይደረባል። ያለነው በሦስተኛው ዓለም ውስጥ ብቻ ሳይሆን በጨለማው የነፋስ ሌሊት ውስጥ ነው።
በውስጣችን ያለውን የኃዘን ጭጋግ የሚገፍ እስካሁን በምድር ላይ አልተገኘም። የብዙዎቻችን ጸሎት እንኳን ከጣራ ጋር እየተላተመ ይመለሳል እንጅ ብዙም አልፈይድ ብሏል። ዛሬ እግዚአብሔር ለምን ዝም አለ?የሚያስጨንቁንንስ ለምን ዝም ይላቸዋል? የሚለው አንደበት ኢትዮጵያ ውስጥ እልፍ ነው። እውነት እንቆቅልሹስ ምን ይሆን? መቼስ ነው የእንቆቅልሻችን መፍትሔ የሚገኘው?