Monday, December 19, 2016

የእመቤታችን ዘላለማዊ ድንግልና

Image result for ethiopian mary
የእመቤታችን ዘላለማዊ ድንግልና በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
(John Chrysostom. C.349-407) Archbishop of Constantinople
=====================================
ቅዱስ ዮሐንስ በዘመኑ ለተነሱት መናፍቃን የድንግል ማርያምን ዘላለማዊ ድንግልና እውነታውን አስረግጦ አስተምሮአል። መናፍቃን "ዮሴፍ የበኩር ልጇን እስከ ምትወልድ አላወቃትም የሚለውን "ማቴ1፣25። ተብሎ ስለተጻፈ ድንግል ማርያም ጌታን ከወለደች በኋላ ከዮሴፍ ጋር በትዳር ኖራለች ብለው ለተነሱበት የተሳሳተ ሃሳብ ሲመልስ፣እስከ የሚለው ሃረግ ወይም ቃል " ዮሴፍ የበኩር ልጇን እስከምትወልድ አላወቃትም ማለት አንድም ወንድ እንደማታውቅ አንድም እስከ የሚለው ፍጻሜ የሌለው እስከ ነው ፤ በመሆኑም ጌታን እስከምትወልድ የምትወልደው መድኃኔዓለምን እንደሆነ አላወቀም፣ የድኅነት ምክንያት ሆና እንደተመረጠች አያውቅም ነበር፣ በሉቃስ ወንጌል ላይም ማርያም ነገርን ሁሉ በልቧ ትጠብቀው ስለነበር ከቅዱሳን የከበረች ከመላዕክትም የበለጠች እንደነበር አያውቅም ነበር ። በሌላው ጌታን በፀነሰች ጊዜ ገጽዋ ይለዋወጥ ነበር ይህንንም ሲያይ ዮሴፍ ጻድቅም ስለነበር ሳይገልጣት ተዋት።

የድንግል ማርያም ክብር

Image result for mary ethiopia

የድንግል ማርያም ክብርና ነገረ ክርስቶስ በቅዱስ አትናቴዎስ ሊቀጳጳስ ዘአሌክሳንድርያ  ( d.373)
======================================================
የድንግል ማርያምን አስተምህሮ (Mariology) ንጽህና ቅድስና ዘላለማዊ ድንግልና እንዲሁም በነገረ ድኅነት ውስጥ ያላትን ሱታፌ አብራርተው ከጻፉትና ካስተማሩት አበው ሊቃውንት መካከል 20ኛው የአሌክሳንድርያው ሊቀ ጳጳስ ቅዱስ አትናቴዎስ አንዱ ነው። ቅዱስ አትናቴዎስ ከመንፈሳዊ መልዕክቶቹ ጠጣርነት በተለይም በነገረ መለኮትና በነገረ ማርያም ትምህርቱ የተነሳ ታላቁ አትናቴዎስ ሐዋርያው አትናቴዎስ እየተባለ ይጠራል። ትክክለኛውን የተዋሕዶ ምስጢር በተለይም የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን የባህርይ አምላክነት ለአርዮስና ለተከታዮቹ አስረግጦ በማስተማሩ የእንዚናዙ ቅዱስ ጎርጎርዮስ "የቤተክርስቲያን አምድ" የሚል ስያሜ ሰጥቶታል።
ቅዱስ አትናቴዎስ በአሌክሳንድርያ በ295 ዓ.ም. ተወለደ፣ ዕድሜው ከፍ ሲልም በ24 ዓመቱ (319 ዓ.ም) ከሊቀ ጳጳሱ ከብፁዕ አቡነ አሌክሳንደር ዲቁናን ተቀበለ፣ የሊቀጳጳሱም ጸሐፊ ሆኖ ተሾመ። ይህ አጋጣሚ ነበረ አትናቴዎስን ከሊቀጳጳሱ ጋር በ325 በተደረገው የኒቂያ ጉባኤ ላይ እንዲገኝ የረዳው።

Sunday, December 11, 2016

መቅደስ እንተ ውስቴታ መቅደስ

በዓታ ለማርያም

ኦ መቅደስ ዘኮነ ለሊሁ እግዚአብሔር ሊቀ ካህናት ማኅየዊ ፤ ጌታ በማኅፀን ያደረብሽ አማናዊት መቅደስ አንቺ ነሽ።
ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ 
ኢያቄምና ሐና ከዘመናት በኋላ በስተርጅና እንደ ፀሐይ የምታበራ ልጅ በመውለዳቸው " ነያ ሠናይት እንተ ኅቤየ ነያ ሠናይት አዕይንትኪ ዘርግብ ሥዕርትኪ ከመ መርኤተ አጣሊ ፤ወዳጄ ሆይ እነሆ ውብ ነሽ እነሆ መልከ መልካም ነሽ ዓይኖችሽ እንደ ርግቦች ናቸው " (መኃ 4፣1) በማለት ሰሎሞን እንደ ዘመረላት ፤ በውስጥ በአፍአ ደም ግባቷ ያማረ 
"ኲለንታኪ ሠናይት እንተ ኅቤየ አልብኪ ነውር ወኢምንትኒ ላዕሌኪ" ተብሎ የተተነበየላትን ፣ፈጣሪዋን የምትመስል ንጽህት ቅድስት ልጅ ስለ ወለዱ አምላክን አመሰገኑ። ኢያቄምና ሐና ደስታቸው ያለምክንያት አልነበረም ፤ አንድም ለረጅም ዘመናት ልጅ ሳይወልዱ ሲያዝኑ ቆይተው" ጸኒሐ ጸናሕክዎ ለእግዚአብሔር ሰምዐኒ ወተመይጠኒ ወሰምዐኒ ቃለ ስእለትየ" እንዲል ነቢዩ ዳዊት፤ እግዚአብሔር ስዕለታቸውን መሻታቸውን አይቶ በእርግናቸው ይህችን ብላቴና በማግኘታቸው እንጅ ቀድሞ ሐና በጎረቤቶቿ ጽርፈት ነበረባት፣ የበቅሎ ዘመድ ኅፁተ- ማኅፀን፤ ማኅፀኗ የተዘጋ እየያተባለች ትሰደብ ነበር ኋላ ይህን ዘለፋ የምታስወግድ ልጅ ወለደች፤ ድንግል ማርያም እንባቸውን አበሰችላቸው ፤ ስድባቸውን አራቀችላቸው ፤በእመቤታችን ነቃፊዎቿን አሳፈረች።