Thursday, November 1, 2012

ማንኛውም ክርስቲያን ሊያውቅ የሚገባ ፍሬ ጥቅሶች።




በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን መሠረት 5ቱ ሀብታት፣ 5ቱ ፍኖተ ጽድቅ፣ 5ቱ አቀብተ ሲኦል፣ 5ቱ ፍኖተ ኃጢአት፣ 5ቱ ሐራ ሲኦል ነገስታት፣ 5ቱ ህሩያነ ነገስታት፣ 5ቱ አርዕስተ አበው ሲባሉ እነሱም፤
፩. †♥†5ቱ ሐብታት የተባሉት፤†♥†
፩.፩ ሐብተ ፈውስ፣  ፩.፪  ሐብተ ክህነት፣  ፩.፫ ሐብተ ትንቢት፣ ፩.፬  ሐብተ መዊእ፣      ፩.፭  ሐብተ መንግስት ናቸው።
...
፪. †♥† 5ቱ ፍኖተ ጽድቅ የተባሉት፣ †♥†
፪.፩ ፍቅር ፪.፪ ትህትና ፪.፫ ጾም ፪.፬ ጸሎት ፪.፭ ምጽዋት ናቸው
፫. †♥† 5ቱ አቀብተ ሲኦል የተባሉት፣†♥†
፫.፩ ጣኦትን ማምለክ ፫.፪ አፍቅሮ ንዋይ ፫.፫ ተጣልቶ አለመታረቅ ፫.፬ ሰው መግደል ፫.፭ እናት አባትን አለማክበር ናቸው።
፬. †♥† 5ቱ ፍኖተ ኃጢአት የተባሉት †♥†
፬.፩ ትዕቢት ፬.፪ ስስት ፬.፫ ምቀኝነት ፬.፬ ስርቆት ፬.፭ ዝሙት ናቸው።
፭. †♥† 5ቱ ሐራ ሲኦል ነገስታት †♥†
፭.፩ ፈርኦን በኤርት የሰጠመው ፭.፪ ሰናክሬም ፭.፫ አንጥያኮስ ፭.፬ ሔሮድስ ፭.፭ ዲዮቅልጥያኖስ ናቸው።
፮. †♥† 5ቱ ህሩያነ ነገስታት የተባሉት †♥†
፮.፩ ህዝቅያስ ፮.፪ ኢዮስያስ ፮.፫ ዳዊት ፮.፬ ሰለሞን ፮.፭ ንግስተ ሰባ አዜብ ማክዳ ናቸው።
፯. †♥† 5ቱ አርዕስተ አበው የተባሉት †♥†
፯.፩ አዳም ፯.፪ ሄኖክ ፯.፫ ኖህ ፯.፬ አብርሃም ፯.፭ ሙሴ ናቸው።
ለወደፊትም አደዳድስና አንባብያን ማወቅ ያለባቸውን አስደናቂ የቤተ ክርስቲያን ታሪኮችን ይዤላችሁ ብቅ እላለሁ ለዚህም የድንግል ማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን አሜን።
†♥† ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣኝ፣ ካለማወቅ ወደ መረዳት ያደረሰኝ አነሳስቶ ላስጀመረኝ አስጀምሮ ላስፈጸመኝ ጥንት ላሌለው ቀዳማዊ ፍጻሜ ላሌለው ድህራዊ ያልኖረበት ጊዜ የሌለ የማይኖርበት ጊዜም የማይኖር የዘላለም ንጉስ ሁሉን ቻይ ፈጣሪ እግዚአብሔርን በራስ ፀጉሬ ቁትር በአጥንቶቼም ልክ አመሰግናለሁ፡፡ እድሜ ለንሰሐ ዘመን ለፍሰሃ ሰጥቶኝ ይህችን ታህል ስለ አባታችን እንድመሰክር የረደኝ አምላክ ስሙ የተመሰገነ ይሁን።
†♥† አመስግኛት የማልሰለች፣ ስለሷ ተናግሬ የማይደክመኝ፣ በሰማይ ያሉ መላእክት በምድርም የሚኖሩ የአዳም ዘር ሁሉ የሚያመሰግኗት በአማላጅነቷ ሁል ጊዜ የማትለየኝ ከፀሐይ ሰባት እጅ የምታበራ የብርሃን እናት የሁሉ እመቤት የአምላክ እናት ከተመረጡ የተመረጠች ከተለዩ የተለየች ከተከበሩ የተከበረች እናቴ እመቤቴ ድንግል ማርያም በቃላት ልገልጸው ከምችለው በላይ አመሰግናለሁ፡፡
†♥† ሌሊትና ቀን ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እያሉ የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔርን የሚያመሰግኑና ሳይሰለቹ የሚጠብቁን ሊቀነ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ቅዱስ ገብርኤል ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱስ ዑራኤል ቅዱስ ራጉኤል ቅዱስ ፋኑኤል እልፍ አእላፋት የሆኑ ጠባቂ መላእክት ሳመሰግን በደስታ ነው፡፡


†♥† በጸሎታቸው ያልተለዩኝን ጻድቃን አባቶቼን አቡነ ተክለሃይማኖትን አቡነ ገብረምንፈስ ቅዱስን አቡነ ሀብተማርያምን አቡነ አረጋዊን አቡነ ኪሮስንና ሌሎች ቅዱሳን አባቶቼን እንዲሁም እናቶቼን ቅድስት ክርስቶስ ሰምራን ቅድስት አርሴማን ብዙ ያልጠቀስኳቸው ቅዱሳንን ለማመስገን ቃላት የለኝም፡፡

†♥† በሰማኝትነታቸው የጥንካሬ ምሳሌ የሆኑልኝ በጸሎታቸው የረዱኝን ቅዱሳን ሰማዕታት ቅዱስ ጊዮርጊስን ቅዱስ እስጢፋኖን መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስንና ሌሎችን ቅዱሳን ሰማዕታትን ሁሉ በእጅጉ አመሰግናለሁ ለዘላለሙ አሜን፡፡
                           †♥† ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለም ዓለም አሜን፡፡ ወአሜን ለይኩን ለይኩን፡፡

ምንጭ፡- የኢትዮጵያውያ ተወላጆች ቅዱሳን ታሪክ በሊቀ ብርሃናት መርቆሬዎስ አረጋ።



No comments:

Post a Comment