Saturday, April 23, 2016

ሆሳዕና





እስራኤላውያን ጌታ የተቀመጠባት አህያ አከበሩ፡ ይህ ትውልድ ግን ጌታ የተቀመጠባት እመቤታችን ማክበር ተሳነው፡፡(ማቴ ፳፩፤ ፩፣ ፱)
============================================================================
• ጌታችን የታሰሩ አህዮች ለምን መረጠ?
•ሐዋርያት ለምን ልብሳቸው አነጠፉለት ?
• ጌታ ለምን በፈረስ ላይ አልተቀመጠም?
•ዘንባባ የምን ምሳሌ ነው?
• በሆሣዕና በእጃችን እደ ቀለበት ማሰራችን የምን ምሳሌ ነው?
---------------------------------------------------------------------

Saturday, April 16, 2016

አማን አማን ዕብለከ ዘኢተወልደ ዳግመ ኢይሬእያ ለመንግስተ እግዚአብሔር(ዮሐ ፫፣ ፫)


ኒቆዲሞስ :
የአብይ ጾም ሰባተኛ ሳምንት
------------------------------------------
ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ መንግስተ ሰማይን አይወርስም::(ዮሐ ፫፣ ፫)
=======================================
ወሀሎ አሐዱ ብእሲ እምፈሪሳውያን ዘስሙ ኒቆድሞስ ። ብዙኃን አምኑ ቦቱ ብሎ ነበርና ብዙኃን ካላቸው ከፈሪሳውያን ወገን የሚሆን ኒቆዲሞስ የሚባል አንድ ሰው ነበር ። መጽሐፍ ይህን ሰው መልአኮሙ ለአይሁድ ይለዋል። መልአክ ማለት አለቃ ማለት ሲሆን ፤ ኒቆዲሞስ የአይሁድ አለቃ የተባለበት ምክንያት አንድም በትምህርቱ በዳኝነት ወንበር ላይ ተቀምጦ ይፈርድ ስለነበር፣ አንድም በሹመቱ የአይሁድ አለቃ ስለነበር፣
አንድም በሃብቱ በንብረቱ ባለጸጋ ስለነበር ነው።

Sunday, April 10, 2016

ሰሙነ ሕማማት --(ክፍል-ሁለት)


ነስአ ደዌነ ወፆረ ሕማመነ
-------------------------
እናት የወለደችው ልጇን እንደምታዝል አምላካችን እኛን ፍጥረቶቹን በተለይም በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረንን ልጆቹን ከልጅነት እስከ እውቀት ከነኃጢያታችን በማይዝል ትከሻው ተሸክሞ የሚያኖረንን መጋቢና ኤልሻዳይ አምላክ አይሁድ በእለተ አርብ መከራ አጸኑበት ተዘባበቱበት ። የአዳም ዘር ክብር ጎድሎት ጸጋው ተገፎ ከሰውነት ተራ ቢወጣ እሱ ሥግው ሆኖ በአጭር ቁመት በጠባብ ደረት ተገለጠ እንደሰው እየተመላለሰ እንደ እግዚአብሔር ሰራ የሰውን ስብዕና ይመልስ ዘንድ ድውያኖቻቸውን ቢፈውስ እውራኖቻቸውን ቢያበራ እነሱ ግን ሰንበትን ሻረ ብለው ክስ መሰረቱበት ፣ ችግራቸውን ይፈታ ዘንድ መናን አበርክቶ በመገባቸው ግፈኞች አይሁድ ግን የበሉበትን ወጪት ሰበሩ በጠላትነት ተነስተው ንጹህ ደም አፈሰሱ( መዝ ፵ ፣፱) ። ስለ በደላችንና ስለ ኃጢያታችን አስራ ሦስት ሕማማተ መስቀልን ተቀበለ። መከራ መቀበሉስ እንዴት ነው ቢሉ በአባቱ ፈቃድ በራሱ ፈቃድ በባሕሪ ሕይወቱ በመንፈስ ቅዱስ ፈቃድ ፍቅር አገብሮት የፍጥረቱ የአዳም ነገር ግድ ስለሆነበት እንጅ እሱ የልዑላን ልዑል የማይገሰስ የማይደፈር ነው ።

Saturday, April 9, 2016

በጥቂቱ ታምነሃልና በብዙ እሾምሃለሁ፤ማቴ ፳፭ ፣፳፩

ገብርኄር 


የአብይ ጾም ስድስተኛ ሳምንት
 ገብርር ማለት ታማኝ አገልጋይ ማለት ነው።
ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ  
ወሕግከኒ በማዕከለ ከርስዬ 
 ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበረ ዐቢይ።
(መዝ፴፱፣ ፰)




 ወምዕመን ዘበኅዳጥ፣ ዘበውኁድ ምዕመነ ኮንከ ዲበ ብዙኅ እሰይመከ። ማቴ ፳፭ ፣፳፩
===============================================
ወደ ሩቅ ሀገር የሚሄድ ባለጸጋ ሰው አገልጋዮቹን ወደ እርሱ ጠርቶ ያለውን ገንዘብ ነግደው እንዲያተርፋበት ሰጣቸው ፣ ቦ ለዘወሀቦ ሃምስተ መክሊተ  አምስት መክሊት የሰጠው ሰው አለ፣ወቦ ለዘወሀቦ ክልኤተ መክሊተ ፡ሁለት መክሊት የሰጠው ሰው አለ፣ወቦ ለዘወሀቦ አሐደ መክሊተ ፡አንድ መክሊት የሰጠው ሰው አለ፤ ለእያንዳንዳቸው እንደአቅማቸው ሰጥቷቸው ሄደ፡ወነገደ በጊዜሃ።
፩) አምስት መክሊት የተቀበለው ወጥቶ ወርዶ አተረፈ ፣ወረብኃ ካልዓተ ኀምስተ መካልየ፤ አምስት አትርፎ አስር አድረገ።
፪) ወከማሁ ዘሂ ክልኤተ መካልየ ረብኃ ካልአተ መካልየ፣እንደዚሁ ሁሉ ሁለት መክሊት የተቀበለውም ወጥቶ ወርዶ አትርፎ አራት አደረገ።
፫) ወዘ አሐደሰ መክሊተ ነስአ ሖረ ወኃለፈ ወከረየ ምድረ ወኃብ ወርቀ እግዚኡ፣ አንድ መክሊት የተቀበለው ግን ሌባ ቢሰርቀኝ ወንበዴ ቢቀማኝ ቀጣፊ ቢያታልለኝ ብሎ ፈርቶ ሄዶ ምድር ቆፍሮ የጌታውን ወርቅ ቀበረ።
ወእምድኅረ ብዙኅ መዋዕል አተወ እግዚኦሙ ለእሉ አግብርት፣ ከብዙ ዓመት በኋላ የእነዚያ አገልጋዮች ጌታቸው መጣ
ወአኅዘ ይትሐሰቦሙ ፡ ተቆጣጠራቸውም።

ተዘጋጅታችሁ ኑሩ ፣(ማቴ ፳፬ ፣፵፪)

ደብረ ዘይት 


የዓብይ ጾም ፭ኛ ሳምንት

ትግሁ እንከ እስመ ኢተአምሩ በዓይ ሰዓት ይመጽእ እግዚእክሙ።(ማቴ ፳፬ ፣፵፪)
===============================================
ወእንዘ ይነብር እግዚእነ ውስተ ደብረ ዘይት ቀርቡ ኅቤሁ አርዳኢሁ ፤ ጌታችንና መድኃኒታችን በደብረዘይት ተቀምጦ ሳለ ደቀመዛሙርቱ ወደሱ ቀርበው ፤ ወይቤልዎ እንተ ባሕቲቶሙ ፤ለብቻቸው ጠየቁት ፡ ንገረነ ማዕዜ ይከውን ፡ -
1)ዝንቱ ወናሁ ይትኃደግ ለክሙ ቤትክሙ በድወ ብሎ ነበርና፤ህንፃ በህንፃ ላይ ሳይፈርስ አይቀርም
2) ወምንትኑ ተአምሪሁ ለምጽአትከ ፣ አማን እብለክሙ ኢትሬእዩኒ፣ የሰውን ልጅ በክብሩ ሲመጣ ታዩታላችሁ ብሎ ነበርና
3) የመምጫህስ ወለኀልፈተ ዓለም ፣ የኀልፈተ ዓለምስ ምልክቱ ምንድን ነው? አሉት።
ጌታችንም የዓለምን መጨረሻና የመምጣቱን ምልክት በዝርዝር አስተማራቸው ፣ ወአውሥአ ወይቤሎሙ 

Thursday, April 7, 2016

ሰሙነ ሕማማት --(ክፍል አንድ)


ነስአ ደዌነ ወፆረ ሕማመነ 
===============
የጌታችንን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራ በትንቢት መነጽር እያየ ነቢዩ ኢሳይያስ መርገማችን ሊሽር ነውራችን ሊያንከባልል ፣ ስለ እኛ የከፈለውን ውለታ ሲዘክር ሕመማችን ታመመ መቅሰፍታችን ተሸከመ ስድባችንን ያስወግድ ዘንድ እሱ ተሰደበ አለ፤ ትውልዱ ግን አላስተዋለም፣ ከትውልዱ ማን አስተዋለ ፣ እርሱ ግን ያከብረን ዘንድ ተዋረደ ፣ ያነሳን ዘንድ ወደቀ
ከእስራታችን ይፈታን ዘንድ በገመድ ታሰረ
በአይሁድ ቀያፋ በስምንቱ ቤተ ጭፍራ ተዘለፈ ፣አስራ ሦስቱን ሕማማተ መስቀል ተቀበለ፡-

Tuesday, April 5, 2016

ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ? (ሆሴ ፲፫፣፲፬)





ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ? (ሆሴ ፲፫፣፲፬)
===================================
ይህንን ቃል ነቢዩ ሆሴዕ የጌታችንን የመድኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ በትንቢት መነጸር እያየ በእምነት ሐሴት እያደረገ ሞት ሆይ መውጊያህ የት አለ? ሲዖል ሆይ ድል መንሳትህስ ወዴት ነው?በማለት ተናግሮታል፡፡
መጽሐፍ እግዚአብሔር ሞትን እንዳልፈጠረም ነገር ግን የሰው ልጆች ትዕዛዝን በመሻር ሕግን በመተላለፍ በአመጽ ምክንያት በሥራቸው ሞትን ወደ ሕይወታቸው እንዳስገቡ ይነግረናል፡፡ ይህንን ሲያጸና ሐዋርያው ጳውሎስም ኀጢዓት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ ካለ በኋላ በኀጢዓትም ሞት ገባ ይለናል፡(ሮሜ ፳፫) የኀጢዓት ደሞወዝ ሞት ነውና ከዚያን ጊዜ ጀምሮ  ሺህ  መቶ ዓመታት ሞት ገዥ ሆኖ : አሳዳጃችን በአንገታችን ላይ ነው ተብሎ እንደተጻፈ በሰው ልጆች ላይ ሁሉ ንጉሥ ሆኖ ኖረ  የአዳም ልጆችም ከሞት እርግማን የተነሣ አልቃሾች ሆነው ኖሩ ደስታ ከእነሱ ራቀ፣ ሞት ሁሉን እያሸነፈ ሁሉን እየማረከ ከተወደደችው ዓመት ደረሰ (ኢሳ ፷፩ )  በዚች ዓመት ግን ነገር ተገለበጠ የተቆጠረው ባዔ የተነገረው ትንቢት ጊዜ በደረሰ ጊዜ ሞት በእባብ ተሰውሮ ገዥ ሆኖ እንደኖረ ከሦስቱ ቅዱስ አንዱ ቅዱስ እግዚአብሔር ወልድ ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ከዙፋኑ ዝቅ ብሎ ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሁለተኛው አዳም ሆነ እንደ እግዚአብሔርነቱ እየሰራ ሞትን በሞት ያጠፋ ዘንድ ሰው ሆነ ከሙላቱ ሳይጎድል በተለየ አካሉ ሰው ሆነ፤ ሰው ሆነው ተፈጥረው ሰው መሆን ያቃታቸውን፣ የሰው ልጆችን ሰው ያደረግ ዘንድ ሰው ሆነ ችግራችንን ይፈታ ዘንድ መርገማችን ይሽር ዘንድ ስድባችን ያስወግድ ዘንድ ሰው ሆነ በግዕዘ ሕፃናትም በሞገስና በጥበብ ቀስ በቀስ አደገ በ፴ዘመኑም በዮርዳኖስ ተጠመቀ ሳይውል ሳያድር ዳመ ቆሮንጦስ ጾመ ጸለየ ከዲያብሎስም ተፈተነ ከዚህም በኋላ ነበረ አሳሪውን ያስር ዘንድ ኀይለኛውን ያንበረክክ ዘንድ ከምድር ከፍ ከፍ አለ (ዮሐ፲፪፴፪) በመስቀል ላይም ተሰቀለ፣ ሁሉን ወደእርሱ ይስብ ዘንድ ሕዝቡን ይቤዣቸዋል ተብሎ በነቢያት ተነግሮ ነበረና ቃሉ ይፈጸም ዘንድ በመስቀል ላይ ተሰቀለ፣ በኃጢዓታችን ሙታን ነበርንና በክርስቶስ ሕይወትን ይሰጠን ዘንድ እስከ መስቀል ሞት ድረስ አከበረን መቃብራችንን ከፍቶ ከሞት ያወጣን ዘንድ ወደ መቃብር ወረደ፣ ሙታንን ሕያዋን ያደርግ ዘንድ ሞተ፣ ሁሉን ሕያው ያደርግ ዘንድ አንዱ ስለሁሉ ሞተ፣ የትንሣኤያችን በኩር ይሆን ዘንድ አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ (፪ቆሮ )::

እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አድሮ የሚሰራው ስራ እጹብ ድንቅ ነው:

 እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አድሮ የሚሰራው ስራ እጹብ ድንቅ ነው:
====================================


የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በሃይማኖት ምሰሏቸው::እብ 13:7
እግዚአብሔር የጸጋ ሁሉ ባለቤት ነው ስለዚህ ለፍጥረቱ የሚሰጠው የጸጋ አይነት ውስን ስፍር ቁጥር ልናበጅለት አንችልም:: የምናውቅበት መንገድ ግን አለን ይህውም በየጊዜው ለሚነሱ ቅዱሳን የሚሰጠውን ጸጋ መመልከት ብቻ ነው:: እግዚአብሔር በቅዱሳኑ አድሮ የሚሰራው ስራ እጹብ ድንቅ ነው:: በመሆኑም በገድላቸውና በታምራቸው ለህሊና የሚያስደንቅ ነገሮችን እንመለከታለን:: በቅዱሳን ገድል ላይ ያሉት ቃል ኪዳኖች መረዳትና የነእርሱንም ስም በመጥራት እግዚአሔርን መማጸን በረከትን ያሰጣል::ለምሳሌ ነብየ እግዚአብሔር ኤልሳን ብንመለከት አምላከ ቅዱስ ኤልያስን በመጥራት በመጠምጠሚያው ባህር ተከፈሎለታል ከዚህ የምንረዳው የቅዱሳንን ስም በመጥራት አምላከ ቅዱሳንን ብንማጸነው የእነርሱን ዋጋ እንቀበላለን ማለት ነው::
በዚህም መሰረት የቅዱሳንን ገድል ጽፎ ማስቀመጥና ትውልድ ከእነርሱ ህይወት እንዲማር ማድረግ ከብሉይ ኪዳን ጀምሮ የነበረ በአዲስ ኪዳንም የነበሩ አበው ለኛ ያቆዩልን የቤተክርስቲያን መንፈሳዊ ሃብት እንጂ ልብ ወለድ ድርሰት አይደለም::