Tuesday, June 3, 2014

ክርስቲያናዊ ሥነምግባር



ክርስቲያናዊ ሥነምግባር
አጠቃላይ ፈተና

‹‹ንዌጥን በረድኤተ እግዚአብሔር››
1.  ከአስርቱ ትዕዛዛት ይመደባል
ሀ/ ህገ-ልቡና
ለ/ አትስረቅ
ሐ/ የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው
መ/ ሁሉም
2.  እግዚአብሔር ከሥራው ሁሉ ስላረፈ ይህንን ቀን ቀደሰው………………….
ሀ/ ቀዳሚውን ሰንበት
ለ/ የመጀመሪያውን ቀን
ሐ/ እሁድን ዕለት
መ/ ሁሉም



3.  የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ነው
ሀ/ በዓለማዊ ዘፈን የእግዚአብሔርን ስም መጥራት
ለ/ ያለምክንያት መጥራት
ሐ/ በአምልኮ ጣዖት
መ/ በሐሳዊ ትንቢት
ሠ/ ሁሉም
4.  የሐሰት አባት ተብሏል በመጽሐፍ ቅዱስ
ሀ/ ይሁዳ          ለ/ ዴማስ          ሐ/ ዲያብሎስ
መ/ አርዮስ
5.  ከሚከተሉት አንዱ ሐሰተኛ ምስክር ነው
ሀ/ ሐሳውያን ነቢያት
ለ/ አርዮስ
ሐ/ መናፍቃን
መ/ ሁሉም
6.  ይህ ሕግ የሰው ልጅ በተፈጥሮው ከእግዚአብሔር ያገኘው ሕግ ነው
ሀ/ የቤተመንግስት ሕግ
ለ/ የፍታብሔር ሕግ
ሐ/ ኢ.ጽሑፋዊ ሕግ
መ/ ሁሉም
7.  ጽሑፋዊ ሕግ በመባል ይታወቃል
ሀ/ የብሉይ ሕግ (አሥርቱ ትዕዛዛት)
ለ/ የሐዲስ ሕግ (ስድስቱ ቃላተ ወንጌል)
ሐ/ ሕገ-ልቡና ፣ ሕገ- ህሊና
መ/ ሀ ና ለ
8.  የሚሰርቅ ሰው ምክንያቱ ………………………….. ነው፡፡
ሀ/ የእምነት (ሃይማኖት) አለመኖር
ለ/ እግዚአብሔርን አለመፍራት
ሐ/ ስግብግብነት፣ ድኅነት፣ ልምድ
መ/ ሁሉም
ሠ/ ለ ና ሐ
9.   ጌታችን ትምህርቱን (አንቀጸ ብፁዓንን) ለምን በተራራ ላይ አስተማረ
ሀ/ የቀድሞ ህግ በተራራ ስለተሰጠ ያንን ሕግ የሰጠሁት እኔ ነኝ ሲል
ለ/ የክብሩን ነገር ሊገልጽ
ሐ/ ተራራ ከፍ እንዲል እነሱም ልባቸው ከፍ እንዲል በምድራዊ ነገር እንዳይታለሉ
መ/ ሁሉም
ሠ/ መልስ የለም
10.  የብፁዓን አዋጆች ብዛት ሲዘረዘር……………………
ሀ/ ስድስት         ለ/ አሥር                ሐ/ ሦስት
መ/ ዘጠኝ
11.  አንቀጸ ብፁዓን የተባለው የትምህርት ክፍል የሚከተሉትን ያካትታል
ሀ/ ምፅዋት፣ ጾም፣ ጸሎት
ለ/ ሕግጋተ ወንጌል
ሐ/ የብፁአን አዋጆች
መ/ ጠቃሚ ሕጎች
ሠ/ ሐ ና ለ
ረ/ ሁሉም
12.  ‹‹የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው መጽናናትን ያገኛሉ›› (ማቴ 5፡4) የሚለው ምን ለማለት ነው?
ሀ/ ስለ ኀጢዓት እያሰቡ ማዘን
ለ/ ስለ ባልንጀራ ኀጢዓት እያሰቡ ማዘን
ሐ/ በሥጋ ስለሞተ ሰው እያሰቡ ማዘን
መ/ ስለ ምድራዊ ሀብትና ስልጣን መጥፋት ማዘን
ሠ/ ሀ ና ለ               ረ/ ሁሉም
13.  ‹‹ፅድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብፁዓን ናቸው ይጠግባሉና›› ማለት ምን ማለት ነው?
ሀ/ ፀሎትን የሚናፍቁ
ለ/ ቃሉን መስማት የሚናፍቁ
ሐ/ ወደ እግዚአብሔር ቤት መሔድ የሚናፍቅ
መ/ ንስሐ ለመግባት የሚናፍቅ
ሠ/ ሁሉም
ረ/ መልስ የለም
14.  ለእግዚአብሔር አገልግሎት የሚውሉ የእግዚአብሔር ሀልዎት መገለጫ የሚሆኑ የጽድቅ ሥራዎች ………………… ናቸው
ሀ/ ጾም፣ ጸሎት፣ ምጽዋት
ለ/ ፈሪሃ እግዚአብሔር ፣ ሃይማኖት፣ ተስፋ
ሐ/ ቅድስና፣ ንጽሕና፣ ፍቅር
መ/ ሀ ና ለ        ሠ/ ሁሉም
15.  ከሰይጣን ፈተና ለመውጣትና ድል ለመንሳት……….ማድረግ ያስፈልጋል
ሀ/ ዘወትር ተግቶ ከልብ መጸለይ (ማቴ 26፡41)
ለ/ ፈቃደ እግዚአብሔር መገዛት (ያዕ 4፡7)
ሐ/ ነቅቶ፣ ተግቶና፣ ታጥቆ መቆም (1ጴጥ 5፡7)
መ/ ልማዳዊ፣ ስሜታዊ ኀጢዓትን በቶሎ መሠረዝ
ሠ/ ሀ ና ለ                     ረ/ ሁሉም
16. ኀጢዓት በአራት ይከፈላል እነሱም…………………………
ሀ/ ጥንተ አብሶ
ለ/ የግል ኀጢዓት
ሐ/ የጋራ ኀጢዓት
መ/ ሥርየት ያለውና ፣ ይቅርታ የሌለው
ሠ/ ሀ ና መ                    ረ/ ሁሉም
17. …………………………… ሰዎችን የሚመለከቱ የጽድቅ ሥራዎች ናቸው፡፡
ሀ/ ጥበብ፣ ንቃት፣ ትህትና፣ ትዕግስተኝነት
ለ/ ገርነት (ደግነት)፣ አስተዋይነት፣ ጽጉዕነት (ጽናት)
ሐ/ ሰላማዊነት፣ ልግስና፣ እውነተኛነት
መ/ ልበ ሰፊነት፣ ደስተኛነት፣ ታማኝነት
ሠ/ ጨዋነት፣ ህዳጌ በቀል (ይቅርባይነት) ፣ አማኝነት
ረ/ መ ና ሠ              ሰ/ ሁሉም                ሸ/ ሀ ና ሐ
18.  ኀጢዓት ………………………… ነው
ሀ/ አለመታዘዝ
ለ/ አመጽ
ሐ/ በጎ ነገርን አውቆ አለመስራ ነው
መ/ ሁሉም               ሠ/ ሀ ና ለ               ረ/ መልሱ የለም
19.  ጽድቅ ማለት ምን ማለት ነው?
ሀ/ በፍጹም መንፈሳዊ ሕይወት መኖር
ለ/ በሰይጣን ላይ መሰልጠን (ድል መንሳት)
ሐ/ በእግዚአብሔር ምስጋና ጸንቶ መኖር
መ/ በእምነት ጸንቶ መኖር
ሠ/ ሀ ና ሐ                    ረ/ ሁሉም
20.  የአመንዝራነት ሕይወት ያልሆነው የትኛው ነው?
ሀ/ ሴሰኝነት              ለ/ የአምልኮተ ጣዖት
ሐ/ ዝሙት               መ/ መልሱ የለም
21.  ሐሰት የሚፈጸምበት መንገድ ነው
ሀ/ የተሳሳተ ፊርማ        ለ/ ጽሑፍ                ሐ/ አንደበት
መ/ ሁሉም               ረ/ መልሱ የለም
22.  ሰው በሐሰት የሚመሰክረው ከሚከተሉት በየትኛው ምክንያት ነው?
ሀ/ በይሉኝታ             ለ/ በዘረኝነትና በጥቅም      ሐ/ መጽሐፋዊ ስለሆነ
መ/  ሁሉም              ሠ/ ሀ ና ለ
23.  አታመንዝር የሚለው ሕግ የተሰጠበት ዓላማ ነው
ሀ/ በዋጋ ስለተገዛን፣ በሥጋችን እግዚአብሔርን ማክበር ስላለብን
ለ/ አመንዝራነት እንሰሳዊ ፀባይ ስለሆነ
ሐ/ አዕምሯችን እንድንጠብቅ
መ/ አመንዝራነት የክርስቲያኖች ግብር ስለሆነ
ሠ/ መልሱ የለም
ረ/ ከ ‹‹መ›› በቀር ሁሉም
24.  የአመንዝራነት መንስኤዎች ናቸው
ሀ/ መጠጥና ምንዝር ጌጥ               ለ/ ጾምና ጸሎት ማብዛት
ሐ/ ፓርቲ፣ ጭፈራ፣ ዘፈን              መ/ ሁሉም
ሠ/ ሀ ና ለ
25.  ‹‹ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ እናንተ ሚስቶች ጠጉርን በመሸረብና ወርቅን በማንጠልጠል ወይም ልብስን በመጎናጸፍ በውጭ የሆነ ሽልማት አይሁንላችሁ›› 1ጰጥ 3፡3 ‹‹በውጭ የሆነ የማይገባ ሽልማት የተባለ ምንድን ነው?››
ሀ/ ቅንድብን መሸለምና የአፍንጫ ጌጥ፣ ፀጉር ቀለም
ለ/ ከመጠን በላይ የሆነ ጌጣጌጥና ጥፍር ቀለም
ሐ/ ኢ-ክርስቲያናዊ የሆነ ንቅሳት
መ/ ሁሉም               ሠ/ መልሱ የለም          ረ/ ለ ና ሐ
26.  በህገ-ወጥ የዝሙት ሥራ (አመንዝራነት) ክቡር የሆነ ሥጋውን የሚያረክስ ሁሉ
ሀ/ በሃይማኖት ሕግ ይጠየቃል
ለ/ በፍትሐ እግዚአብሔር ይመረመራል
ሐ/ ለህግ አጥፊዎች የተወሰነው ቅጣት ይጠብቀዋል
መ/ ሀ ና ለ              ሠ/ ሁሉም               ረ/ መልሱ የለም
27.  አመንዝራነት የሚያስከትለው ጉዳት………………… ነው
ሀ/ ሞትና ጋህነል እሳት
ለ/ መርከብና መዋረድ
ሐ/ ባርነትና የአካል፣ የአእምሮ ድክመት
መ/ መልሱ የለም                      ሠ/ ሀ ና ለ               ረ/ ሁሉም
28.   ሰው አትስረቅ የሚለውን ሕግ ተላልፎ ከ …………………………… ይሰርቃል
ሀ/ ከራሱ ይሰርቃል (ኅሊናን በመሸጥ)           ሐ/ ከእናትና ከአባት
ለ/ ከባልንጀራው ከእግዚአብሔር                መ/ ከድኃው
ሠ/ ለ ና ሐ                                ረ/ ሁሉም
29.  የሰው ልጅ እንዳይሰረቅበት ሊንከባከባቸውና ሊጠብቃቸው የሚገቡ ሦስት ነገሮች ምንድን ናቸው?
ሀ/ ሕይወት፣ ትዳርና፣ ንብረት
ለ/ ወርቅ፣ ብርና፣ ልብስ
ሐ/ መጽሐፍ፣ ጋዜጣና፣ መጽሔት
መ/ ሀ ና ለ              ሠ/ ሁሉም
30. ሰው የሌሎችን ሐብትና ንብረት የሚሰርቅበት ጥበብ ነው
ሀ/ በሚዛን፣ በስፍር፣ በልውውጥ ማጭበርበር
ለ/ በመዝረፍ
ሐ/ አራጣና ጉቦ በመቀበል
መ/ ለሠራተኛ ከሚገባው በታች በመክፈል
ሠ/ ሀ ና ሐ
ረ/ ሁሉም
31. ……………………………….. ሰዎች ትዳርን (ሕይወትን) የሚሰርቅበት ዘዴ ነው
ሀ/ ጥቅማጥቅም ፣ ገንዘብ
ለ/ የተሳሳተ መረጃ (በመዋሸት)
ሐ/ እምነት ማጉደል
መ/ ጉልበትና ስልጣን መከታ በማድረግ
ሠ/ ሀ ና ለ                           ረ/ ሁሉም
32.   ‹‹ጌታችን ነፍሳትን የሚሰርቁትን ሌቦች ይላቸዋል›› (ዮሐ 10) ለመሆኑ እንዴት ይሰርቃሉ?
ሀ/ በኑፋቄ፣ በሐሰት ትምህርትና ትንቢት
ለ/ ወደ ኀጢዓት መንደር ወደ ሞት መንደር በመውሰድ
ሐ/ በማገትና በአካል በመስረቅ
መ/ ሀ ና ለ                    ረ/ ሁሉም
33.   የሰው ልጅ ከሚሰርቅባቸው ምክንያቶች አንዱ ነው
ሀ/ ከልምድና ከችግር የተነሣ
ለ/ ከጥጋብና ውንብድና የተነሣ
ሐ/ ለደባል ሱስ ተገዥ በመሆን
መ/ በአልጠግብ ባይነት
ሠ/ ሀ ና ለ                           ረ/ ሁሉም
34.  ‹‹ስለ ጽድቅ መሰደድ›› …………………ን ያጠቃልላል
ሀ/ ስለጽድቅ መነቀፍን
ለ/ በውሸት መታማትን
ሐ/ መጠላትን
መ/ መልሱ የለም
ሠ/ ሁሉም
35.  …………………………….. ከስድስቱ ቃላተ ወነወጌል አይመደብም
ሀ/ የሚምሩ ብፁዓን ናቸው ይማራሉና
ለ/ የሚያዝኑ ብፁዓን ናቸው መጽናናትን ያገኛሉና
ሐ/ ታምሜ ጎበኛችሁኝ
መ/ ተርቤ አበላችሁኝ
ሠ/ ሁሉም                     ረ/ ሀ ና ለ
36.   ……………………. ከብፁአን አዋጆች አይመደብም
ሀ/ ተርቤ አብልታችሁኛል
ለ/ የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው
ሐ/ ታርዤ አልብሳችሁኛል
መ/ በመንፈስ ድሆች ብፁዓን ናቸው
ሠ/ ሁሉም ይመደባሉ
ረ/ ሀ ና ሐ
37.   አንቀጸ ብፁአን የተባለውን ትምህርት ማን አስተማረ ይህ ትምህርት ………………. በሚል ስያሜም ይጠራል
ሀ/ ኢየሱስ፣ ህገ ኦሪት
ለ/ ጳውሎስ፣ የተራራው ስብከት
ሐ/ ክርስቶስ፣ አንቀጸ ወንጌል
መ/ ኢየሱስ፣ የተራራው ስብከት
ሠ/ ጴጥሮስ፣ አንቀጸ ብፁዓን
38.  ከሚከተሉት አንዱ ትክክል አይደለም
ሀ/ አንቀጸ ብፁዓን የሐዲስ ኪዳንን ሕግ የያዘነው
ለ/ የሐዲስ ኪዳን ሕግ የመንፈስ ሕግ ይባላል
ሐ/ የሐዲስ ኪዳን ሕግ ቱርፋት ይባላል
መ/ የሐዲስ ኪዳን ሕግ በጻሐፍት የተሰጠ ስለሆነ ለብሉይ ኪዳን ሕግ መፈጸሚያ ነው
ሠ/ የሐዲስ ኪዳንም ሆነ የብሉይ ኪዳን ሕግ በተራራ ላይ የተሰጠ
39.   ‹‹በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው›› ማለት ምን ማለት ነው?
ሀ/ በትህትና የሚኖሩ
ለ/ ሁሉ እያላቸው እንደ ሌላቸው የሚሆኑ
ሐ/ ዓለም ከንቱ መሆኗን ተረድተው ዓለምን የተው
መ/ ሁሉ የእግዚአብሔርና በእግዚአብሔር መሆኑን አምነው የሚኖሩ
ሠ/ ሀ ና ለ               ረ/ ሁሉም
40.  ‹‹የዋሆች ብፁዓን ናቸው›› ማለት …………………….. ነው
ሀ/ መብትን ለሌላው አሳልፎ መስጠት ለራስ አለመሟገት
ለ/  ቂም በቀል አለመያዝ
ሐ/ በክርስትና ሕይወታቸው ጠቢብ የሆኑ
መ/ ዓላማ ያላቸው         ሠ/ ሀ ና ለ               ረ/ ሁሉም
41.  አስርቱን ትዕዛዛት ዘርዝረህ ጻፍ

42.  የብፁዓን አዋጆችን ዘርዝር


43. ሕገ- ወንጌልን (ቃለተ-ወንጌል) የሚባሉትን ዘርዝር



ወስብሐት ለእግዚአብሔር

1 comment: