Thursday, January 11, 2018

ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተክርስቲያን አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት




የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን         
==========================

===>ቤተ ኢያኢሮስ የፈውስና የድህነት ቤት ናት ፣አንድም ቤተ ሳህል የምህረት አደባባይ ዘማዊው ድንግል፣ቀማኛው መጽዋች ኀጥኡ ጻድቅ ሆኖ የሚቀየርባት ናት
==>የእግዚአብሔርን ልጅ መድኅን ዓለም ክርስቶስን ለማየት ብቸኛዋ የዘኪዮስ ሾላ፣ አምስት እንጀራና ሁለት አሣ በርክቶ የተመገበባት የጥብርያዶስ ባሕር ማቴ ፲፬፣፲፱
==>የመጀመሪያዋ የዓለማችን መንፈሳዊት የደን ሚኒስቴር አጸዶቿ በገነት አምሳል በተለያዩ ዕፅዋቶች የለመለመች፣
==>ሕመምተኞች በመንፈሳዊ ሐኪሞች ተመርምረው ፈውስና ድህነት የሚያገኙባት መንፈሳዊት ላቦራቶሪ (ማቴ፱፣፴፮)፤
==>በእግዚአብሔር ልጅ የሚያምኑ ከአብራከ መንፈስ ቅዱስ ከማህፀነ ዮርዳኖስ ዳግመኛ የሚወለዱባት (ዮሐ፫፣፭)፤
==>ለሚያምኑት ሁሉ የእግዚአብሔር ልጅ ይሆኑ ዘንድ አባት ብለው የሚጠሩበትን የልጅነትን ክብር የሚያገኙባት፣ ከሰማዊው ምስጢር ተሳታፊ የሚሆኑባት፤
==>የእግዚአብሔር የፀጋው ግምጃ ቤት በሚታይ አገልግሎት የማይታይ ጸጋ የሚታደልባት ፤
የጥበብ ቤት ሰባቱ ምሰሶዎች የተዘረጉባት
በአምስቱ አዕማድ ጸንታ የታነጸች፤
==>የመጀመሪያዋ የትምህርት ሚኒስቴር ፊደል ቀርጻ ብራና ዳምጣ ትውልዱን ያስተማረች፣ የሀገር ኩራት ፊደልን ቀርጻ በቅርስነት ያበረከተች፤
==>የሒሳብ ስሌት ሰርታ የዘመን ሳይንስ ቀምራ አበቅቴና መጥቅን ለይታ የአጿማትና የበዓላትን ዕለታት ወስና የዘመን መቁጠሪያ አዘጋጅታ ለትውልድ ያበረከተች የጥበብ ተቋም፣
==> ምግባራቸውን ያቀኑ ፣ሃይማኖታቸውን ያጸኑ አርአያና ምሳሌ የሚሆኑ፣ ሀገርና ሕዝብ ወዳድ ትውልድን ያፈራች ብቸኛዋ የስነ ዜጋ ትምህርት ቤት
==>እንባ የሚታበስባት ታሪክ የሚቀየርባት ነውር የሚንከባለልባት፣ እንቆቅልሽ የሚፈታባት፣ በትህትና የሆኑ ጻድቃን የሚገቡባት የደብረዘይት ተራራ፤
==>ቅዳሴ የሚቀደስባት፣ ሰዓታትና ማህሌት የሚቆምባት፣የእግዚአብሔር ምስጋና አውድ፤
==>ዘመን የሚሻገር ከትውልድ ትውልድ የሚተላለፍና የሚወረስ ቁሳዊና ራዕያዊ ትውፊትና ቅርስ ያላት
==> ሁሉ ያላት ሁሉ የተረፋት ስንዱ እመቤት ብታውስ እንጅ የማትበደር ፣ ያልተበረዘ ያልተከለሰ ንጹህ ወንጌል የሚሰበክባት፣
==> በነቢያትና በሐዋርያት ላይ የተመሠረተች በማዕዘኑ ራስ ድንጋይ በክርስቶስ የጸናችና የታነጸች፤(ኤፌ፪፣፳)
==>አንድም በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የታነፀች በቅዱሳን ያሸበረቀች በሰማዕታት ደም የከበረች፣
==> ኢየሱስ ክርስቶስ ከባሕሪ አባቱ ከአብ ከባሕሪ ሕይወቱ ከመንፈስ ቅዱስ የተካከለ አምላክ መሆኑ የሚሰበክባት፣
==> የእመ አምላክ የወላዲተ ቃል የድንግል ማርያም ክብርና አማላጅነት የሚታመንባትና የሚነገርባት፣
==>የቃል ኪዳኑ ታቦት ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ለማክበር ና ትውልዱን ለመባረክ በቅድስተ ቅዱሳኗ የሚገኝባት፣ የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ምሳሌ ናት።
-----------------------------------------------------
የካቲት ፳፬ቀን ፳፻፰ዓ.ም.
መምህር.ዲ.ቸርነት ይግረም

No comments:

Post a Comment