Saturday, January 30, 2016

ሞት የተሸነፈብሽ ሆይ ሞት እንዴት አገኘሽ


    ሞት የተሸነፈብሽ ሆይ ሞት እንዴት አገኘሽ
    =========================

                         " ሞትሰ ለመዋቲ ይደሉ
                            ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኩሉ
    ትርጉም ፦ ሞትማ ለሚሞት ሰው ይገባዋል
    የማርያም ሞት ግን እጅግ ያስገርማል"

    የመላዕክት እህት ሆይ መውጊያው የተሰበረ ሞት እንዴት በአንቺ ላይ በረታ፤
    የአዳም ተስፋው የአብርሃም ርስቱ ክብርት ሆይ ፍላፃው የተቆረጠ ሞት እንዴት በአንቺ ላይ ኃይል አገኘ፤
    የአመፃ መዝገባችንን የገለበጠውን ብርቱ የወለድሽ ሆይ ደካማው እንዴት ወደ አንቺ መጣ፤...
    በብርሃን ላይ ስልጣን ያለውን ብርሃንን የወለድሽ ሆይ የጨለማው አበጋዝ እንዴት አንቺን ደፈረ፤
    የፍቅርና የትህትና መምህርት ሆይ የጥልና የትዕቢት አባት ሞት እንዴት አገኘሽ፤
    ርግበ-ኖህ የተባልሽ የድኅነታችን ምክንያት ሆይ ከሐዲው ቁራ ወደ አንቺ ለምን መጣ፤
    መዓዛሽ የተወደደ የናርዶስ ቀጺመታት ሽቱ ሆይ ክፋ ጠረንና መጥፎ ሽታ ያለው እንዴት አንቺን ቀረበ፤
    የነቢያትን ናፍቆት የወለድሽ የኢሳይያስ ድንግል የሕዝቅኤል የተዘጋ ምስራቅ በር ሆይ በምን በኩል የተናቀው አገኘሽ፤
    የዮሐንስ እናት ደግሞም የጥበቡ ምንጭ ሆይ የማትሞቺ እንዴት አንቺ ሞትሽ፤
    ሐዘናችንን ያራቅሽ ሙኃዘ ፍስሐ የተባልሽ የደስታችን መፍሰሻ ሆይ የሐዘናችን ምክንያት መላከ ሞት አንቺን ይቀርብ ዘንድ እንዴት እድል አገኘ፤
    ሞት የተሸነፈብሽ አንቺ ሆይ ከቶ ሞት እንዴት ወደ አንቺ መጣ፤


    ጥር ፳፩ ቀን፳፻፰ ዓ.ም


No comments:

Post a Comment