Thursday, November 12, 2020

 ምክረ ቅዱሳን

ሀ) "ራስህን በሐሰት አትውቀስ:: ራስን መክሰስ ትህትና አይደለም ታላቁ ትህትና ሰዎች ሲወቅሱህ መታገስ ነው::" /ቅዱስ ስራፕዮን/
ለ) "የማታምንበትን ነገር ለሰው ስትል አትስራው ከሰራኸው እንደምትጠፋበት እወቅ፡፡" /መጽሐፈ ምክር/
ሐ) "አንደበቱን ከቧልት ከሐሜት ያየውንም ምስጢር ከመናገር የሚከለከል ሰው ልቦናውን ከኀልዮ ኃጥያት ያርቀዋል፡፡" /አረጋዊ መንፈሳዊ/
መ) "ጸጋ ቢሰጥህ በተሰጠህ ጸጋ አመስግን ያልተሰጠህን እሻለሁ በማለት የተሰጠህን እንዳታጣ፡፡" /ማር ይስሐቅ/
ሠ) "ራሱን የሚንቅ የሚያቃልል ሰው ከእግዚአብሔር ዘንድ እውቀትን ያገኛል አዋቂ ነኝ የሚል ሰው ከፈጣሪው ጥበብ ይለየዋል፡፡" /አረጋዊ መንፈሳዊ/
ረ) "እግዚአብሔር ሆይ አፈርና ትቢያ ሆኜ ሳለ ጻድቅ አድርገው ከሚቆጥሩኝ ሰዎች አድነኝ::" /አባ እንጦንስ/
ሰ) "ፍጡራንን መርምሮ ማወቅ ካልተቻልን ሁሉን የፈጠረ እርሱን መርምሮ ማወቅ እንደምን ይቻለናል?" /ቅዱስ አትናቴዎስ/
ሸ) "ወርቅ በእሳት እንደሚፈተን ሁሉ የክርስቶስንም ፀጋና ክብር ሳይፈተኑ ማግኘት አይቻልም:: የዚህ ዓለም ፈተናና እሳት ቶሎ ያልፋል ይጠፋል ኃጢያተኞች የሚገቡበት የገሀነም እሳት ግን ለዘለዓለም እንደ ነደደ ይኖራል::" /ቅዱስ ሚናስ/


No comments:

Post a Comment